የኮሚሽነር ጄኔራል መልዕክት

Commissioner Image

የተከበራችሁ ውድ የሀገራችን ህዝቦች፣ የተከበራችሁ መላው የሃገራችን ፖሊስ አመራር እና አባላት እንዲሁም አጋር የፀጥታ አካላት በአሁኑ ወቅት ሀገራችን ኢትዮጵያ በፖለቲካ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የለውጥ ሂደት ላይ ትገኛለች።

ዝርዝር መልዕክት

አዳዲስ ዜናዎች!

  • የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ወንጀል መከላከል ጠቅላይ መምሪያ “በኢትዮጵያ ሉዓላዊነት መቼም የትም አንደራደርም” በሚል መሪ ቃል የዕውቅና እና የምስጋና መርሃ-ግብር አካሄደ( Federal News)

    አዲስ አበባ ጥቅምት 10 ቀን 2017 ዓ.ም (ኢ.ፌ.ፖ.ሚ) የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ወንጀል መከላከል ጠቅላይ መምሪያ የ2016 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸምን አስመልክቶ "በኢትዮጵያ ሉዓላዊነት መቼም የትም አንደራደርም" በሚል መሪ ቃል የዕውቅና እና የምስጋና መርሃ-ግብር በሚሊኒየም አዳራሽ አካሂዷል::

    ክቡር የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል በፕሮግራሙ ላይ ባደረጉት ንግግር የወንጀል መከላከል ጠቅላይ መምሪያ ከዚህ ቀደም ባልተለመደ ሁኔታ በታድሶ ፕሮግራሙ ጀግኖቹን የሚያወድስበት፤ የሚሰሩትን የሚያመሰግንበት፤ ከለውጡ በኋላ እያደገ የመጣ ትልቅ ፕሮግራም በመሆኑ ተሞክሮ የሚወሰድበትና ሁሉም ከዚህ የሚማርበት መሆኑን ገልፀው ለመላው የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ሠራዊት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

  • የፈጥኖ ደራሽ ፖሊስና የፀጥታና ተቋማት ጥበቃ ዋና መምሪያ አመራርና አባላት የተቋሙን የሪፎርም ስራዎች ተዙዋዙረው በመጎብኘት ለጀግኖች ማዕከል የ60 ሺህ ብር ድጋፍ አደረጉ( Federal News)

    አዲስ አበባ ጥቅምት 10 ቀን 2017 ዓ.ም (ኢ.ፌ.ፖ.ሚ) በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ወንጀል መከላከል ጠቅላይ መምሪያ የፈጥኖ ደራሽ ፖሊስ እና የፀጥታና ተቋማት ጥበቃ ዋና መምሪያ አባላት የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የሪፎርም ስራዎችን ለሁለት ቀናት ተዘዋውረው ጎብኝተው ለፌደራል ፖሊስ ጀግኖች ማዕከል የ60ሺህ ብር ድጋፍ አድርገዋል።

    ክቡር የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አዛዥ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል በጉብኝት ላይ የነበሩትን አመራርና አባላት ባወያዩበት ወቅት ፖሊስ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት ያለው ሙያ መሆኑን አንስተው በታሪክ ሊመዘገብ የሚችል ሥር ነቀል ለውጥ ማምጣት የቻልነው ዩኒሸርሲቲያችንን የጥናትና ምርምር ማዕከል በማድረጋችን ነው ሲሉ ለጉብኝት ተሳተፊዎች ገልጸዋል።

  • የአፍሪካ የመከላከያ ሚኒስትሮች የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስን የለውጥ ሥራዎችን ጎበኙ( Federal News)

    አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 7 ቀን 2017 ዓ.ም (ኢፌፖሚ) የአፍሪካ የመከላከያ ሚኒስትሮች በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ዋና መሥሪያ ቤት ተገኝተው የለውጥ ሥራዎችን ጎብኝተዋል፡፡

    ክቡር የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል የአፍሪካ የመከላከያ ሚኒስትሮችን በደማቅ ፖሊሳዊ ስነ-ስርዓት ተቀብለው ባደረጉት የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር አፍሪካውያን ወንድሞቻችን እና እህቶቻችን ወደ ኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ዋና መሥሪያ ቤት ለጉብኝት በመምጣታችሁ የተሰማኝን ደስታ እገልፃለሁ ብለዋል፡፡

  • ከኢትዮጵያ ፖሊስ፣ ከሪፐብሊካን ጋርድ ጥበቃ ኃይልና ከሌሎች የፀጥታ ተቋማት ለተውጣጡ ከፍተኛ አመራሮች በቻይና ሀገር ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ተጠናቀቀ( Federal News)

    ቻይና ቤጂንግ፣ መስከረም 4 ቀን 2016 ዓ.ም (ኢፌፖሚ)  ከኢትዮጵያ ፖሊስ፣ ከሪፓብሊካን ጋርድ ጥበቃ ኃይል፣ ከኢትዮጵያ አርተፊሻል ኢንተለጀንስ እና ከኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ለተውጣጡ ከፍተኛ አመራሮች በቻይና ሪፐብሊክ ወንጀል ምርመራ ፖሊስ ዩኒቨርስቲ ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ተጠናቀቀ።

    ክቡር የቻይና ሪፐብሊክ ወንጀል ምርመራ የፖሊስ ዪኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዚደንት ዊ ሸንግዋንግ በስልጠና መዝጊያ ሥነ-ሥርዓት ላይ ባደረጉት ንግግር የፖሊስ ሥልጠና መርሃ ግብሩ በኢትዮጵያና በቻይና የፖሊስ ተቋማት መካከል እንደ ድልድይ ሆኖ የነበረውን መልካም ግንኙነትና ተግባቦት ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግር ገልፀዋል።

  • ጉዳት ደርሶባቸው በህክምና ላይ ለሚገኙ የፖሊስ አመራርና አባላት የበዓል ስጦታ ተበረከተላቸው( Federal News)

    አዲስ አበባ፣ ጳጉሜ 5 ቀን 2016 ዓ.ም (ኢፌፖሚ) የሕዝብን ሰላምና ደኅንነት ለማስፈን በተለያዩ የሀገራችን አከባቢዎች ተሰማርተው ከፀረ-ሰላም ኃይሎች ጋር በጀግንነት ሲፋለሙ ጉዳት ደርሶባቸው በፖሊስ ሪፈራል ሆስፒታል በህክምና ላይ ለሚገኙ የፌደራልና የክልል ፖሊስ አመራሮችና አባላት የበዓል ስጦታ ተበረከተላቸው።

  • “በደም በአጥንታቸው ሀገርን አፅንተው ሉዓላዊት ሀገር ለአስረከቡን ምስጋና ይገባቸዋል” ክቡር ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር ተመስገን ጥሩነህ( Federal News)

    አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 3 ቀን 2016 ዓ.ም ኢ.ፌ.ፖ.ሚ፡- የሉዓላዊነት ቀን “ኅብር ለሁለንተናዊ ሉዓላዊነት” በሚል መሪ ሀሳብ በመላ ሀገሪቱ ተከበረ፡፡

የሚሰጡ አገልግሎቶች

የሚሰጡ አስተዳደራዊ አገልግሎቶች


  1. ጥቆማና አቤቱታ መቀበልና የአቅራቢዎችን ቃል መቀበል
  2. የህዝብ ክንፍ መድረክ በማዘጋጀት የዜጎችን መረጃ የማግኘት መብት ማረጋገጥና የተቋሙን አፈጻጸም እንዲገመግሙ ማድረግ


በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የሚሰጡ አገልግሎቶች


  1. የማህበረሰብ አገልግሎት (Community Service) ስራዎችን ማከናወን፣
  2. ስለወንጀል መከላከልና ምርመራ ሀገር አቀፍ ፖሊሲዎችን፣ ስትራቴጂዎችንና አንድ ወጥ የሆኑ የአሠራር ደረጃዎችን ማዘጋጀት


በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ጤና አገልግሎት የሚሰጡ አገልግሎቶች


  1. የተመላላሽ ህክምና አገልግሎት ለሰራዊቱና ለህግ ታራሚዎች መስጠት፤
  2. የተኝቶ ህክምና አገልግሎት መስጠት


በወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ የሚሰጡ አገልግሎቶች


በክስ መቀበል አገልግሎት

  1. የወንጀል ጥቆማዎችንና አቤቱታዎችን መቀበል፣
  2. የቀረበው አቤቱታ ጥቆማ ወንጀል መሆን አለመሆኑን እና በፌደራል የማጣራት ስልጣን ስር የሚወድቅ መሆን አለመሆኑን መወሰን፣